አበባን በሜዳ

አበባን በሜዳ የሚያፈካ
ዘመንን በዘመን የሚተካ
የሚለዉጥ በጋ ክረምትን
እግዚአብሔር ይመስገን
ወራትን በክረምት አሰናድቶ
አሮጌዉን ዘመን አሰናብቶ
ፀሃይን ሲያወጣ በጊዜያቱ
ድንቅ ነዉ እግዚአብሔር ለፍጥረቱ
ሰማይን በደመናት አልብሶ
ምድርን በነጠብጣብ አረስርሶ
ልምላሜን የሰራ በጊዜያቱ
መጋቢ ነዉ አምላክ ለፍጥረቱ
አበቦች በተራራ ሲያበሩ
አእዋፍ ስለክብሩ ዘመሩ
ጸሐይም በሰማይ ስትወጣ
ደስ አለን አዲስ አመት ሲመጣ
ሰማይን በደመናት አልብሶ
ምድርን በነጠብጣብ አረስርሶ
← መዝሙር