አዳምን ሊያድነው

አዳምን ሊያድነው ጌታችን ወደደ
ነፍስና ሥጋሽን ነስቶ ተዋሐደ
በአባቱ ፈቃድ ከሰማይ ወረደ
እንደ ተስፋ ቃሉ ከአንቺ ተወለደ
ይኸው ይኸው ተወለደ መድኅን
ድምጹንም ሰማነው በጎለ እንስሳ
ምንኛ ድንቅ ነው የይሁዳ አንበሳ
በአንቺ ተመስርቶ ፍቅርና ሰላም
በአንድ ላይ አደሩ አንበሳና ላህም
ይኸው ይኸው ተወለደ መድኅን
ድንግል እመቤቴ የንጉሥ አገሩ
ለአዳም ተስፋው ነሽ ለኖህም ሐመሩ
የሰው ልጆች ሁሉ ተዋርደው ሲኖሩ
ከሞት ወደ ሕይወት በአንቺ ተሻገሩ
ይኸው ይኸው ተወለደ መድኅን
አዳምም ለመዳን አነባ አለቀሰ
ወደ ጥንተ ክብሩ በአንቺ ተመለሰ
በአንቺ ተፈጽሞ የአባቶች ተስፋ
ፍዳችን ተሻረ መርገማችን ጠፋ
ይኸው ይኸው ተወለደ መድኅን
← መዝሙር