አደባባይ ቆሜ
✦
አደባበይ ቆሜ ስምህን ከመስበክ
መጀመሪያ ልቤ ከፊትህ ይንበርከክ
ከአገልግሎት በፊት አንተን ልወቅህ
መሥዋዕት ከማቅረብ ልታዘዝልህ፪
መጀመሪያ ልቤ ከፊትህ ይንበርከክ
ከአገልግሎት በፊት አንተን ልወቅህ
መሥዋዕት ከማቅረብ ልታዘዝልህ፪
አሐዱ አብ ብዬ ስምህን ብቀድስ
ለድሆች ብሰጥ ቤትህ ብገሰግስ
በመላእክት ልሳን ብዘምር በእልልታ
ምን እጠቅማሃለሁ ካልፈራሁ ጌታ፪
ለድሆች ብሰጥ ቤትህ ብገሰግስ
በመላእክት ልሳን ብዘምር በእልልታ
ምን እጠቅማሃለሁ ካልፈራሁ ጌታ፪
ተራራ እስካፈልስ እምነት ቢኖረኝ
ሥራ ከሌለበት ምንም አይጠቀመኝም
ልቤን ስትመረምር ከሆንኩኝ ቀላል
ክርስቲያን መባሉ ምን ይጠቅመኛል፪
ሥራ ከሌለበት ምንም አይጠቀመኝም
ልቤን ስትመረምር ከሆንኩኝ ቀላል
ክርስቲያን መባሉ ምን ይጠቅመኛል፪
ጨው አልጫ ቢሆን በምን ይጣፍጣል
ከውጭ ተጥሎ በእግር ይረገጣል
አንተን ለሚከተል እንዳልሆን እንቅፋት
አምልኮቴ ይሁን በፍቅር በፍርሃት፪
ከውጭ ተጥሎ በእግር ይረገጣል
አንተን ለሚከተል እንዳልሆን እንቅፋት
አምልኮቴ ይሁን በፍቅር በፍርሃት፪
የዕውቀት ሰው መሆን አልጠቀመኝ
እኔስ መስቀልህ ነው ፍቅርህ ያሸነፈኝ
ከእምነቴ የተነሳ መታዘዝ የሆነኝ
ስምህን መፍራት ነው በእምነት የሚያኖረኝ፪
እኔስ መስቀልህ ነው ፍቅርህ ያሸነፈኝ
ከእምነቴ የተነሳ መታዘዝ የሆነኝ
ስምህን መፍራት ነው በእምነት የሚያኖረኝ፪
✦