ዓለም ወረተኛ

ዓለም ወረተኛ ከዳተኛ ነች
ዛሬ ከአንተ ጋር ናት ነገ ከሌሎች
አምላክ ለመኖሩ እኛ ማሰረጃ ነን
እልፍኝ ያለ ሠሪው በምንም አላየን
አለም ኃላፊ ናት እናስተውል ሰዎች
እንደ ጠዋት ጤዛ እንደጥላችን ነች
አስተውል ወንድሜ በተሰጠህ ተስፋ
ለሥጋህ አድልተህ ነፍስህ እንዳትጠፋ
ሰዎች አንታለል ለሚቀረው ዓለም
እኛስ እናልፋለን ቃሉ ግን አያልፍም
አምላክ የለም ቢሉ የተሳሳቱት
የህልም እሩጫ ነው ከንቱ መዋተት
መራቀቅ ቢበዛ በሆነው ባልሆነው
በቁመቱ ስንዝር የሚጨምር ማነው
← መዝሙር