አልፋና ዖሜጋ

አልፋና ዖሜጋ ፈጣሪ የሆንክ
በከሐዲዎች እጅ ተይዘህ ቀረብክ
ተገረፍህ ተሰቅለህ በጥፊ ተመታህ
እየደበደቡ ተዘባበቱብህ
ጽድቅን ስለሠራህ በወንጀል ከሰሱህ
ለአዳም ቤዛ ብለህ ብዙ ተንገላታህ
ቅዱሳን እችህ የፍጥኝ አሥረው
ሲገርፉህ ክፉዎች ይቅር አልካቸው
የሁሉ ፈጣሪ ሁሉን የምታውቅ
ዘበቱብህ መቱህ ሸፍነው በጨርቅ
በዚህ አደባባይ ከጲላጦስ ዘንድ
አሳልፈው ሰጡህ ጨካኞች ለፍርድ
ከሐና ቀያፋ ከካህናት ደጅ
ከነሄሮድስ ዘንድ አቀረቡህ በአዋጅ
ግርፋት ሕመሙ አልበቃ ብሎህ
መስቀል ላይ ልትውል ተፈረደብህ
ሣዶር እና አላዶር ዳናትና አዴራ
ተፈልገው መጡ ለችካር በተራ
አምስን ችንካሮች ቅንዋተ መስቀል
አይሁድ አመጡ ሥጋህን ለማቁሰል
የሰላም ባለቤት አካልህ ተወጋ
ሊወጋ በችንካር እጅህ ተዘረጋ
ግፈኞች አይደሁድ በአንተ ላይ ቀለዱ
ምራቅን ተፉብሕ አንተን ሊጎዱ
ዘማሪ በየነ ድንቁ፣ ዜማ ኪነ ጥበብ
← መዝሙር