አምላክ ሆይ ወደኛ ባትመጣ
✦
አምላክ ሆይ ወደኛ ባትመጣ ለብሰህ የማርያምን ሥጋ፪
ባክኖ የኖረው የአዳ ዘር ውጤቱ ነበር የሚያሰጋ፪
ባክኖ የኖረው የአዳ ዘር ውጤቱ ነበር የሚያሰጋ፪
በዚያች ዓመት በዚያች ወር በዚያች ቀን
ድህነትን ለሰው ልጅ ስትሰጥ፪
ምን ይበዛ ነበር ትሕትናህ፣ ትዕግሥትህ የማይለወጥ፪
ድህነትን ለሰው ልጅ ስትሰጥ፪
ምን ይበዛ ነበር ትሕትናህ፣ ትዕግሥትህ የማይለወጥ፪
የሾህ አክል ደፍተህ በራስህ ጎንህን ሲወጉህ በጦር፪
አንተ ግን ለነረሱ ካባትህ ምሕረትን ስትጸልይ ነበር፪
አንተ ግን ለነረሱ ካባትህ ምሕረትን ስትጸልይ ነበር፪
ግን መቼ አወቁት እነርሱ በኃጢአት ደንድኖ ልባቸው፪
መድኃኒታቸውን ገረፉህ ሰቀሉህ አንተም ሞትክላቸው፪
መድኃኒታቸውን ገረፉህ ሰቀሉህ አንተም ሞትክላቸው፪
ዳግም ስትመጣ ለፍርድ ከዓለም ፍጻሜ በኋላ፪
እንዴት ዕድለኞች ናቸው ካንተ የሚያኙት ተድላ፪
እንዴት ዕድለኞች ናቸው ካንተ የሚያኙት ተድላ፪
በዚያች በደብረ ዘይት ቦታ ደስታን ለቅሶ ሲፈልቅ፪
ከቶ ወዴት ይሆን ዕድሌ ያንጊዜ የኔ አወዳደቅ፪
ከቶ ወዴት ይሆን ዕድሌ ያንጊዜ የኔ አወዳደቅ፪
የፀፀጽ ሮሮ በፊትህ እንዳያቃጥለኝ እኔን፪
እርዳኝ ፈጣሪዬ ካሁኑ አንጻው የዛገው ልቤን፪
እርዳኝ ፈጣሪዬ ካሁኑ አንጻው የዛገው ልቤን፪
ዘማሪ የሺህ እመቤት
✦