አምላክ ለኛ ብሎ

አምላክ ለኛ ብሎ ቢያፈሰው ደሙን
ለምን ከለከለች ፀሐይ ብሃኗን
አንቺ ዕለተ ዓርብ ከሁሉ በለጥሽ
ለማያልቀው ሥጋ ገበያ ሁነሽ
ከማያለውቀው ሥጋ ሰዎቹ ቢበሉ
ገነት ገብተው ቀሩ ሳይከለከሉ
የከበረው ሥጋ የከበረው ደም
በመስቀል ላይ ዋለ ኢየሩሳሌም
በሥጋችን ሐኪም ዓለም ተታለለ
ነፍስን የሚያድናት ደጉ ሐኪም ሳለ
ይኸው ደጉ ሐኪም የማይፈልግ ዋጋ
ነፍሥንም ሥጋን ያድናል ካደጋ
መዳን የምትፈልግ ላሳይህ ቤቱን
በሰላም ጠይቃት ቤተ ክርስቲያንን
ዘማሪ ዶ/ር ኢሳይያስ ዓለሜ
← መዝሙር