አምላኬ ሆይ አትተወኝ ፈጣሪዮ ተመልከተኝ

አምላኬ ሆይ አትተወኝ ፈጣሪዮ ተመልከተኝ
ምንም ብበድልህ የእጆችህ ሥራ ነኝ
በዓለም ፍላጎት ታሥሬ እንዳልጠፋ
አውጣኝ ከፈተና አንተው ሆነኝ ተስፋ
አዝ.
ሥጋዊ ፈቃዴ ተበረታቶ ነፍሴ እጅጉን ተዳክማለች
የእጆችህን ማዳን ተስፋ ታደርጋለች
አዝ.
የሞትክልኝ አምላክ መድኃኒት ሆነህ መድኃኒት አንተ ለኔ
እንዳይሠለጥኑብኝ ፍዳና ኩነኔ
አዝ.
በሥጋህ በደምህ የገዛⷐኝ የዋጀⷐኝ ጌታ
ኃይል የለኝምና ሁንልኝ መከታ
አዝ.
← መዝሙር