አንቺን የያዘ ሰው
✦
አንቺን የያዘ ሰው ምን ይጎድልበታል
በምልጃሽ በረከት ቤቱ ሞልቶለታል
ዘር መከር ባይኖረው ጎተራው ባይሞላ
ሁሉም ይሸፈናል በረድኤትሽ ጥላ ፪
በምልጃሽ በረከት ቤቱ ሞልቶለታል
ዘር መከር ባይኖረው ጎተራው ባይሞላ
ሁሉም ይሸፈናል በረድኤትሽ ጥላ ፪
በረከትሽ ብዙ የደናግል ገንዘብ
የምስኪናን እናት የርኁባን ቀለብ
ለሁሉ መጋቢ ጸጋሽ የማይጎድል
ስምሽ ጥዑም ምግብ ከረሀብ የሚያስጥል ፪
የምስኪናን እናት የርኁባን ቀለብ
ለሁሉ መጋቢ ጸጋሽ የማይጎድል
ስምሽ ጥዑም ምግብ ከረሀብ የሚያስጥል ፪
አንቺን የያዘ ሰው ምን ይጎድልበታል
በምልጃሽ በረከት ቤቱ ሞልቶለታል
ዘር መከር ባይኖረው ጎተራው ባይሞላ
ሁሉም ይሸፈናል በረድኤትሽ ጥላ ፪
በምልጃሽ በረከት ቤቱ ሞልቶለታል
ዘር መከር ባይኖረው ጎተራው ባይሞላ
ሁሉም ይሸፈናል በረድኤትሽ ጥላ ፪
አንቺ ብትመጪ ከምስኪኗ ቤቴ
እንደ መጥምቁ እናት በዛልኝ ሐሴቴ
የአዲስ ኪዳን ቁርባን መንበር ጠረጴዛ
ጽድቅን አሸተትን የሕይወት መዓዛ ፪
እንደ መጥምቁ እናት በዛልኝ ሐሴቴ
የአዲስ ኪዳን ቁርባን መንበር ጠረጴዛ
ጽድቅን አሸተትን የሕይወት መዓዛ ፪
አንቺን የያዘ ሰው ምን ይጎድልበታል
በምልጃሽ በረከት ቤቱ ሞልቶለታል
ዘር መከር ባይኖረው ጎተራው ባይሞላ
ሁሉም ይሸፈናል በረድኤትሽ ጥላ ፪
በምልጃሽ በረከት ቤቱ ሞልቶለታል
ዘር መከር ባይኖረው ጎተራው ባይሞላ
ሁሉም ይሸፈናል በረድኤትሽ ጥላ ፪
ልቤ ተጠራጥሮ ኪዳንሽን ካልከዳ
ልመናም አልወርድም አልይዝም አኩፋዳ
ሁሉን እየሞላሽ መመገብ ታውቂያለሽ
ቢዝቁት የማያልቅ ጸጋና ሃብት አለሽ ፪
ልመናም አልወርድም አልይዝም አኩፋዳ
ሁሉን እየሞላሽ መመገብ ታውቂያለሽ
ቢዝቁት የማያልቅ ጸጋና ሃብት አለሽ ፪
አንቺን የያዘ ሰው ምን ይጎድልበታል
በምልጃሽ በረከት ቤቱ ሞልቶለታል
ዘር መከር ባይኖረው ጎተራው ባይሞላ
ሁሉም ይሸፈናል በረድኤትሽ ጥላ ፪
በምልጃሽ በረከት ቤቱ ሞልቶለታል
ዘር መከር ባይኖረው ጎተራው ባይሞላ
ሁሉም ይሸፈናል በረድኤትሽ ጥላ ፪
የእግዚአብሔር ማረፊያ ኮሬባዊት ዋሻ
የሕይወት ውሃ ምንጭ የህግ መፍሰሻ
ነበልባል ተዋሕዶሽ ሙሴ አንቺን አይቷል
ጫማውን አውልቆ በፊትሽ ተደፍቷል ፪
የሕይወት ውሃ ምንጭ የህግ መፍሰሻ
ነበልባል ተዋሕዶሽ ሙሴ አንቺን አይቷል
ጫማውን አውልቆ በፊትሽ ተደፍቷል ፪
አንቺን የያዘ ሰው ምን ይጎድልበታል
በምልጃሽ በረከት ቤቱ ሞልቶለታል
ዘር መከር ባይኖረው ጎተራው ባይሞላ
ሁሉም ይሸፈናል በረድኤትሽ ጥላ ፪
በምልጃሽ በረከት ቤቱ ሞልቶለታል
ዘር መከር ባይኖረው ጎተራው ባይሞላ
ሁሉም ይሸፈናል በረድኤትሽ ጥላ ፪
✦