አንድ ጊዜ

አንድ ጊዜ የእግዚአብሔር ሆኛለሁ
በፍቅሩ ተስቤ በደሙ ድኛለሁ
ዓለም ተይኝ ንቄ ትቼሻለሁ
ጥበበኛው ሰይጣን በመጣው ቢመጣ
ዳግም ተመልሼ ከእቅፍህ ላልወጣ
በመስቀሉ ግርጌ አርፌ እኖራለሁ
ዓለም ተይኝ የእግዚአብሔር ሆኛለው
አዝ ---
ቢያሙኝ ቢያጥላሉኝ ቢሳለቁብኝ
ውርደትን ተንኮልን ቢሸርቡብኝ
ለእኔ እንደው ደስታ ነው ሐዘንም የለኝ
ሰይጣን እፈር የክርስቶስ ነኝ
አዝ ---
ጓደኞቼ ጠሉኝ ተለውጬባቸው
የጥንቱን ፀባዬን ስለነፈግኹአቸው
ብቻዬን የሆንኩኝ ቢመስለኝም ለእኔ
ጌታ እንደሆን አለልኝ ከጎኔ
አዝ ---
← መዝሙር