አንደበትን ስጠኝ ጌታዬ

አዳኙ ስምህን ዘወትር ልጠራበት
ቅዱስ ኃያል ህያው ክብር የምልበት
ከሃጢያት የራቀ ሐኬት የሌለበት
ምስጋናህን ብቻ የምናገርበት
አንደበትን ስጠኝ ጌታዬ
ሕይወት የሆነውን ቃልህን ሰባኪ
ገናናነትህን ክብርህን ተራኪ
ለንስሃ ህይወት በጎችህን ጠሪ
እንደ ሐዋሪያት ፍቅርህን መስካሪ
ከከሃድያን ጋር የማይተባበር
ፆምና ጸሎትን የሚያዘወትር
ከጽድቅ ስራ ጋር መልካም ህብረት ያለው
በምድራዊ ምኞት የማይታለለው
ፈተና ሲገጥመኝ በመከራ ጊዜ
የሀዘን ጥላ ጋርዶን ሲከበን ትካዜ
ተመስገን የሚል በችግር በደስታ
ርቱዕ አንደበትን ፍጠርልን ጌታ
← መዝሙር