አርሴማ ቅድስት ወሰማዕት

አርሴማ ቅድስት ወሰማዕት
ወሰማዕት ሰማዕት አርሴማ ቅድስት ኧኸ
ወሰማዕት ሰማዕት አርሴማ ቅድስት
አዝ
ከምድር ሙሽርነት ይበልጣል የሰማይ
በማለት ወሰነች ሰይፍ ስለቱን ሳታይ
የሰማዕትነቷ ፅኑ መከራዋ
ተቀበለችበት የክብርን ፅዋ
ኧኸ ወሰማዕት ሰማዕት አርሴማ ቅድስት
አዝ
የዚህችን ዓለም ጣዕም ፍፁም ያልበገራት
የንጉስ ግልምጫ ከእግዚአብሔር ያልለያት
አምላኳን መረጠች መክሊቷን አትርፋ
አክሊል ተቀዳጀች ለእምነት ተሰልፋ
ኧኸ ወሰማዕት ሰማዕት አርሴማ ቅድስት
አዝ
የማይታየውን ለመውረስ ተብሎ
በሚታየው ዓለም ይበዛል ተጋድሎ
የሰማዕታት ዋጋ ይኸው ነው ውጤቱ
በዚህ ምድር ሳይሆን በሰማይ ነው ቤቱ
ኧኸ ወሰማዕት ሰማዕት አርሴማ ቅድስት
አዝ
ውበት ከንቱ ነው ደምግባት ሀሰት
እንዲህ ብላ ፀናች አርሴማ ቅድስት
ያመነችው ጌታ በሰጣት ቃልኪዳን
ልዩ እናት ሆናለች ትውልዱን በማዳን
አርሴማ ቅድስት ወሰማዕት
ወሰማዕት ሰማዕት አርሴማ ቅድስት ኧኸ
ወሰማዕት ሰማዕት አርሴማ ቅድስት
← መዝሙር