አስታርቂኝ

አስታርቂኝ ድንግል ማርያም
ከልጅሽ ከመድኃኔዓለም
አስታርቂኝ ኃጢአትን ሰርቼ
አስታርቂኝ ጫካ ውስጥ ቆሜአለው
አስታርቂኝ ሥራዬ አሳፍሮኝ
አስታርቂኝ ዘወትር አነባለው
አስታርቂኝ ልጄ አዳም ብሎ
አስታርቂኝ አምላኬ ሲጠራ
አስታርቂኝ እነሆኝ ለማለት
አስታርቂኝ አንደበቴ ፈራ
አዝ ------------
አስታርቂኝ ሀብትን ተካፍዬ
አስታርቂኝ ከገዛ አባቴ
አስታርቂኝ ከቤቴ ኮበለልኩ
አስታርቂኝ ይሻለኛል ብዬ
አስታርቂኝ ገፍቼ ወጥቼ
አስታርቂኝ የቤቴን ገበታ
አስታርቂኝ ልበላ ተመኘሁ
አስታርቂኝ የእንስሳት ገፈራ
አዝ---------
አስታርቂኝ ወደ አባቴ ልሂድ
አስታርቂኝ አሁን ተነሥቼ
አስታርቂኝ ይቅርታ ልጠይቅ
አስታርቂኝ እግሩ ስር ወድቄ
አስታርቂኝ ልጅነቴ ቀርቶ
አስታርቂኝ አድርገኝ ባርያህ
አስታርቂኝ ከሞያተኞችህ
አስታርቂኝ እንደ አንዱ ቆጥረህ
አዝ ------
አስታርቂኝ ገና ሩቅ ሳለው
አስታርቂኝ አባቴ አይቶኝ
አስታርቂኝ ወደእኔ ሮጦ
አስታርቂኝ አቅፎ ነው የሳመኝ
አስታርቂኝ ጠፍቶ የነበረው
አስታርቂኝ ተገኘልኝ አለ
አስታርቂኝ ሞቶ የነበረው
አስታርቂኝ ደግሞ ሕያው ሆነ
← መዝሙር