አየሁት በሕልሜ
✦
አየሁት በሕልሜ (2x)
ሞት የተባለሁን ሥጋ ተሸክሜ2x
ሰማሁት በዝና (2x)
ቀጠሮ አክባሪ ነው ሞት አይቀርምና (2x)
ዓለምን ለማዳን የተሰቀለው
ኢየሱስ ክርስቶስ እግዚአብሔር ነው ፪
ሞት የተባለሁን ሥጋ ተሸክሜ2x
ሰማሁት በዝና (2x)
ቀጠሮ አክባሪ ነው ሞት አይቀርምና (2x)
ዓለምን ለማዳን የተሰቀለው
ኢየሱስ ክርስቶስ እግዚአብሔር ነው ፪
ጌታችን ተሰቅሎ ቢያዩት መላእክት
በዝማሬ ፈንታ አለቀሱለት
ሚካኤል ዝም አለ ገብርኤል ገረመው
አምላኩ እርቃኑን ተሰቅሎ ስላየው፪
በዝማሬ ፈንታ አለቀሱለት
ሚካኤል ዝም አለ ገብርኤል ገረመው
አምላኩ እርቃኑን ተሰቅሎ ስላየው፪
ነፍሱን ለወዳጁ የሚሰጥ ቢገኝም
ለጠላት የሚሞት በጭራሽ አይኖርም
ጠላቶቹ ስንሆን ለኛ የሞተው
ክርስቶስ ልዩ ነው ወደርም የለው፪
ለጠላት የሚሞት በጭራሽ አይኖርም
ጠላቶቹ ስንሆን ለኛ የሞተው
ክርስቶስ ልዩ ነው ወደርም የለው፪
እውርን ቢያበራ የሞተን ቢያስነሣ
በመመስገን ፈንገታ ሆነበት አበሳ
ሰማያዊው ዳኛ ሊፈረድበት
ተከሶ ቀረበ በጲላጦስ ፊት ፪
በመመስገን ፈንገታ ሆነበት አበሳ
ሰማያዊው ዳኛ ሊፈረድበት
ተከሶ ቀረበ በጲላጦስ ፊት ፪
ዐርብ በመስቀል ላይ የተሰቀለው
ሥጋና ደሙን ለእኛ የሰጠው
ፍቅር አስገድዶት ለኛ የሞተው
መልካሙ እረኛችን መድኃኔ ዓለም ነው፪
ሥጋና ደሙን ለእኛ የሰጠው
ፍቅር አስገድዶት ለኛ የሞተው
መልካሙ እረኛችን መድኃኔ ዓለም ነው፪
✦