በእምነታቸው ዳኑ

በእምነታቸው ዳኑ ከዚያ ነበልባል
አናንያ አዛርያ ሚሳኤል
ናቡከደነፆር ጨካኙ ንጉሥ
በባቢሎን ሀገር ጣዖት የሚያነግሥ
እያለ ስገዱ አማኙን ሲያምስ
ወጣቶች ተነሡ በቅናት መንፈስ
አናንያ አዛርያ ሚሳኤል
ለሠራኸው ጣዖት አንሰግድም እያሉ
በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ልባቸውን ሞሉ
የፈጠረን አምላክ ያድናል ሲሉ
አናንያ አዛርያ ሚሳኤል
አዘ ------------
ነበልባል ነዲዱ እንዲያቃጥላቸው
በጭካኔ መንፈስ አስወረወራቸው
ገብተው ሲጸልዩ ፍህሙ ሳይነካቸው
መልአኩን ልኮ አበረደላቸው
ገብርኤል በመስቀል
እንደ ሦስቱ ሕፃናት በእምነት ለሚቆመው
መልአኩን ይልካል እግዚአብሔር ሊረዳው
እሳቱም ይበርዳል መልአኩን ሲልከው
ገብርኤል በመስቀል
በእምነታቸው ዳኑ ከዚያ ነበልባል
አናንያ አዛርያ ሚሳኤል
← መዝሙር