በጌቴ ሰማኔ
✦
በጌቴ ሰማኔ በአታክልቱ ቦታ፪
ለእኛ ሲል ጌታችን በዓለም ተንገላታ፪
አዳምና ሔዋን ባጠፉት ጥፋት፪
እኛም ነበረብን የዘለዓለም ሞት፪
መስቀል ተሸክሞ ሲወጣ ተራራ፪
ይገርፉት ነበረ ሁሉም በየተራ፪
ድንግል አልቻለችም እንባዋን ልትገታ፪
እያየች በመስቀል ልጇ ሲንገላታ፪
በአምላክነቱ ሳይፈርድባቸው፪
እንዲህ ሲል ጸለዬ አባት ሆይ ማራቸው፪
በረቂቅ ስልጣኑ ሁሉን የፈጠረ፪
በረቂቅ ጥበቡ ሁሉን የፈጠረ፪
በሰው እጅ ተገርፎ ሞተ ተቀበረ፪
ለእኛ ሲል ጌታችን በዓለም ተንገላታ፪
አዳምና ሔዋን ባጠፉት ጥፋት፪
እኛም ነበረብን የዘለዓለም ሞት፪
መስቀል ተሸክሞ ሲወጣ ተራራ፪
ይገርፉት ነበረ ሁሉም በየተራ፪
ድንግል አልቻለችም እንባዋን ልትገታ፪
እያየች በመስቀል ልጇ ሲንገላታ፪
በአምላክነቱ ሳይፈርድባቸው፪
እንዲህ ሲል ጸለዬ አባት ሆይ ማራቸው፪
በረቂቅ ስልጣኑ ሁሉን የፈጠረ፪
በረቂቅ ጥበቡ ሁሉን የፈጠረ፪
በሰው እጅ ተገርፎ ሞተ ተቀበረ፪
✦