በኢያሪኮ መንገድ

በኢያሪኮ መንገድ ጌታ አንተ ስታልፍ
ግፊያ ሆኖ ስደነቃቀፍ
የዳዊት ልጅ ማረኝ ብዬ ተማጸንኩህ
ዓይኔንም ፈወስከኝ ዛሬ ማየት ቻልኩኝ
አንተን እንዳላይ ቁመቴ አጠረብኝ
ከፊት እየሮጥኩ ከዛፍ ላይ ወጣሁኝ
ጌታ ሆይ ጠረኸኝ ዘኬዎስ ሆይ አልከኝ
ቤቴ እንድትገባ ፍቃድህ ሆነልኝ
ሐሴትም ሆነልኝ በጣምም ደስ አለኝ
አንተን በእንግድነት በቤቴ ተቀበልኩኝ
ኃጢአቴን ሁሉ በአንተ ፊት ጥያለሁ
ሀብቴን አካፍል ዘንድ እንዲገባ አውቃለሁ
የክፋትን ገንዘብ መስብሰቤን ትቼ
አንተን ልክተልህ ሁሉን ረስቼ
ኑሮዬንም ባርከው የሕይወት ዘመኔን
መርጫለሁ አንተን በቤትህ መኖሬን
← መዝሙር