በክብር ዙፋኑ

በክብር ዙፋኑ መርጦ ያስቀመጠሽ
ለእኛ ለኃጢአተኞች ተስፋችን አንቺው ነሽ
በፍጹም ንጽሕና ቤተመቅደስ ያደግሽ
የአማኑኤል የጌታዬ የፈጣሪ እናት በምን እንመስልሽ
ቃና ዘገሊላ ሠርግ ደግሰው
አንቺን ከነልጅሽ በክብር ጠርተው
ሰዎች ተረብሸው በጣም ተደናግጠው
ወይኑ በማለቁ በፍርሃት ተውጠው
አዝ ---
ወይኑ በመሃል ላይ ማለቁን ሰምተሽ
ድንጋጤአቸውን እመበቴ አይተሽ
ወደ ልጅሸ ሄደሽ ብትጠይቂላቸው
ጋኑን ውኃ ሙሉት ብሎ አዘዛቸው
አዝ ---
ውኃውን ወደወይን አጣፍጦ ቀይሮ
የዶኪማስንም እፍረቱን ሰውሮ
እድምተኞች ሁሉ እስከሚደነቁ
አምላክ ከእነእርሱ ጋር መሆኑን አወቁ
አዝ ---
← መዝሙር