በምን በምን

በምን በምን እንመስላት ድንግል ማርያምን
ምሳሌ የላትም የላትም ክብሯን የሚመጥን/2
የሙሴ ጸላት ነሽ የምሕረት ቃል ኪዳን
የያእቆብ መሠላል የአብርሃም ድንኳን
የብርሃን መውጫ የኖኅ ድንቅ መርከብ
የመላእክት እህት የሩኅሩኀን ርግብ
በምን በምን እንመስላት ድንግል ማርያምን
ምሳሌ የላትም የላትም ክብሯን የሚመጥን/2
የሰሎሞን አክሊል የአሮን በትር
የእዝራ መስንቆ የጌዴዎን ፀምር
ድንግል እመቤት ናት የጻድቃን በር
ሆና የታገኘች የአምላክ ማኅደር/2
በምን በምን እንመስላት ድንግል ማርያምን
ምሳሌ የላትም የላትም ክብሯን የሚመጥን/2
የቅዱሳን እናት የዓለም ንግሥት
ችላ ተሸከመች በሁለት እጇ ይዛ
ብርሃን ትሁነን ጨለማን ገላልጣ
አማልዳ ታስምረን ከዚህ ዓለም ጣጣ
በምን በምን እንመስላት ድንግል ማርያምን
ምሳሌ የላትም የላትም ክብሯን የሚመጥን/2
ከማር ይጣፍጣል የድንግል መዓዛ
አምላክን አቅፋለች በሁለት እጃእ የዛ
ዓለም ሁሉ የዳነው በልጅሽ ነውና
እናታችን ጽዮን ይድረስሽ ምስጋና /2
በምን በምን እንመስላት ድንግል ማርያምን
ምሳሌ የላትም የላትም ክብሯን የሚመጥን/2
← መዝሙር