በንጹህ ደሙ ያዳነን

በንጹህ ደሙ ያዳነን
በንጹህ ደሙ ያዳነን
ከወደቅንበት ያነሳን
ብዙ ነው የእርሱ ውለታ
እንዘምራለን ለጌታ
ቀና ብለናል በክብር
አንገቱን ደፍቶ በፍቅር
ስለኛ ብዙ ሆኖልን
የብርሃን አክሊል ደፋልን
የአለም መድኃኒት ጌታ ነው
ጠላታችንን ያሰረው
እርቃኑን ሆኖ ሸለመን
እየደከመ አቆመን
እርሱ በመስቀል ሲሞት
እኛ ተጻፍን በህይወት
የአለም መድኃኒት ጌታ ነው
ጠላታችንን ያሰረው
እስከ ሺህ ትውልድ ይምራል
ፍቅር ነውና ይራራል
አይዝልም የእርሱ ትከሻ
መጨረሻ ነው መድረሻ
የአለም መድኃኒት ጌታ ነው
ጠላታችንን ያሰረው
በደም ያጌጠ ልብስ አለው
ከአማልክት ማንም አይመስለው
እውልዱ ማዳኑን ይስማ
ነግሷል በጽዮን ከተማ
የአለም መድኃኒት ጌታ ነው
ጠላታችንን ያሰረው
← መዝሙር