ብርሃን የለበሰው
✦
ብርሃን የለበሰው በሰማያት ያለው፪
እንደ እግዚአብሔር ከቶ ማንም የለም፪
ውኆችን በእፍኙ የሠፈረ
ተራሮችን በሚዛን የመዘነ
ሰማይን በስንዝር የሚለካ
ዘመንን በዘመን የሚተካ፪
አዝ ---
ከዓለም በፊት የነበረ
ፍጥረታትን ሁሉ የፈጠረ
በምድር ክብብ የሚቀመጥ
ሁሉን ሲለውጥ የማይለወጥ ፪
አዝ ---
ዙፋኑ የጸና በሰማይ
ሁሉ የሚቻለው አዶናይ
ለመንግሥቱ ፍጻሜ የሌለው
አልፋና ኦሜጋ አምላክ ነው፪
አዝ ---
ከሀሊ ኩሉ ሁሉንም የሚያውቅ
ፈታሄ በጽድቅ ሥራው ረቂቅ
ዓለምን የመላ ፈጥሮ የሚገዛ
መዓቱ የራቀ ምሕረቱ የበዛ፪
እንደ እግዚአብሔር ከቶ ማንም የለም፪
ውኆችን በእፍኙ የሠፈረ
ተራሮችን በሚዛን የመዘነ
ሰማይን በስንዝር የሚለካ
ዘመንን በዘመን የሚተካ፪
አዝ ---
ከዓለም በፊት የነበረ
ፍጥረታትን ሁሉ የፈጠረ
በምድር ክብብ የሚቀመጥ
ሁሉን ሲለውጥ የማይለወጥ ፪
አዝ ---
ዙፋኑ የጸና በሰማይ
ሁሉ የሚቻለው አዶናይ
ለመንግሥቱ ፍጻሜ የሌለው
አልፋና ኦሜጋ አምላክ ነው፪
አዝ ---
ከሀሊ ኩሉ ሁሉንም የሚያውቅ
ፈታሄ በጽድቅ ሥራው ረቂቅ
ዓለምን የመላ ፈጥሮ የሚገዛ
መዓቱ የራቀ ምሕረቱ የበዛ፪
✦