ደም ግባት አልባ

ጌታዬ ሆነ ደም ግባት አልባ፣
ጀርባዉ በጅራፍ ስለኔ ደማ፣
የኔን መገርፍ እረሱ ተገርፎ፣
ክብር አለበሰኝ እርሱ ተገፎ
በሀሰት ሸንጎ ወጥመድ ተጠምዶ፣
ጌታ ተያዘ ህይወቴን ፈቅዶ፣
ክፉዎች ቢያዩት እንደ ወንበዴ፣
ለኔ ግን ሆኗል መዉጫ መንገዴ
ታስረኃል ስለኔ ኢየሱስ መድኅኔ፣
ታስረኃል ስለኔ ኢየሱስ መድኅኔ፣
ጌታዬ ሆነ ደም ግባት አልባ፣
ጅርባዉ በጅራፍ ስለኔ ደማ፣
የኔን መገረፍ እርሱ ተገርፎ፣
ክብር አለበሰኝ እርሱ ተገፎ
ሲዘብቱበት ምራቅ ሲተፉ፣
የማይደፈር ደፍረው ሲዘልፉ፣
በከበቡት ፊት ቃል ከለከለ፣
እኔ እንድናገር እርሱ ዝም አለ
ታርደኃል ስለኔ ኢየሱስ መድኅኔ፣
ታርደኃል ስለኔ ኢየሱስ መድኃኔ ፣
ጌታዬ ሆነ ድም ግባት አልባ፣
ጀርባዉ በጅራፍ ስለኔደማ፣
የኔን መገረፍ እርሱ ተገርፎ፣
ክብር አለበሰኝ እርሱ ተገፎ
ህይወት መንጭቷል ተወግቶ ጎኑን
ለከሳሾቹ ተርፏል ማዳኑ፣
እጅ እግሩን ምስማር ሲቸነክርዉ
የሞትን እሾህ ከኔ ነቀለዉ
ተወጋ ስለኔ ኢየሱስ መድኃኔ፣
ተወጋ ስለኔ ኢየሱስ መድኃኔ፣
ጌታዬሆነ ደም ግባት አልባ፣
ጀርባዉ በጅራፍ ስለኔ ደማ፣
የኔን መገረፍ አርሱ ተገርፎ፣
ክብር አለበሰኝ አርሱ ተገፎ
እርቃኑን ሆኖ ፈተነዉ ልብሴን፣
አንዲሁ ወዶኝ ጠጣ ቆምጣጤ፣
በምህረቱ ጥል ነብሴን አርክቶ፣
አለመለመኝ አርሱ ተጠምቶ
ተጠማ ስለኔ ኢየሱስ መድኃኔ ፣
ተጠማ ስለኔ ኢየሱስ መድኃኔ፣
← መዝሙር