ድንግል ሆይ ስላንቺ

ድንግል ሆይ ስለአንቺ ነውና መሐሪ
አማልጅን ከአንድ ልጅሽ ከፈጣሪ
ስሙን እንዳልጠራ አንደበትም የለኝ
ፊቱንም እንዳላይ ሥራዬ አሣፈረኝ
ድንግል ሆይ ----------------
ታውቆኛል ጥፋቴ ብዙ እንደበደልኩኝ
ትእዛዙን እንደሻርኩ ሕጉን እንደጣስኩኝ
አዝ
አንተ ክቡር መልአክ ልደቱን አብሣሪ
አማልደኝ ከጌታዬ ከፈጣሪ
ድንግል ----------------
በፊቱ እንዳላፍር የተጠራሁ ለታ
እለምነዋለሁ ከአሁኑ ይቅርታ
ጻድቃን ሰማዕታት እናንተ ሁላችሁ
አማልዱኝ ከአምላኬ ከአምላካችሁ
ድንግል ሆይ ------------------
← መዝሙር