ድንግል ትንሣኤሽን
✦
ድንግል ትንሣኤሽን እስከምናይ ድረስ
ገብተናል ሱባኤ በአንድነት በመንፈስ
ለኛ እስከ ሚገለጥ ቶማስ ያየው እውነት
አንወጣም ከደጅሽ ኪዳነ ምሕረት፪
ገብተናል ሱባኤ በአንድነት በመንፈስ
ለኛ እስከ ሚገለጥ ቶማስ ያየው እውነት
አንወጣም ከደጅሽ ኪዳነ ምሕረት፪
ሞትን የረገጠ ልጅሽ ከአንቺ ጋር ነው
ውጦ የሚያስቀርሽ የቱ መቃብር ነው
የዕርገትሽን ዜና ከቶማስ ሰምተናል
ትንሣኤሽ እውነት ነው ሰበንሽን አይተናል
ሞትማ በሞት ተሸንፏል
በአንቺ ላይ እንዴት ኀይል ያገኛል፪
ውጦ የሚያስቀርሽ የቱ መቃብር ነው
የዕርገትሽን ዜና ከቶማስ ሰምተናል
ትንሣኤሽ እውነት ነው ሰበንሽን አይተናል
ሞትማ በሞት ተሸንፏል
በአንቺ ላይ እንዴት ኀይል ያገኛል፪
ድንግል ትንሣኤሽን እስከምናይ ድረስ
ገብተናል ሱባኤ በአንድነት በመንፈስ
ለኛ እስከ ሚገለጥ ቶማስ ያየው እውነት
አንወጣም ከደጅሽ ኪዳነ ምሕረት፪
ገብተናል ሱባኤ በአንድነት በመንፈስ
ለኛ እስከ ሚገለጥ ቶማስ ያየው እውነት
አንወጣም ከደጅሽ ኪዳነ ምሕረት፪
ልናየው ወደድን የቶማስን ክብር
ለምን ተሠወረን የትንሣኤሽ ምስጢር
በራችንን ዘግተን በጸሎት ወድቀናል
ተገልጠሽ አብሪልን ልጆችሽ ናፍቀናል
ሞትማ በሞት ተሸንፏል
በአንቺ ላይ እንዴት ኀይል ያገኛል፪
ለምን ተሠወረን የትንሣኤሽ ምስጢር
በራችንን ዘግተን በጸሎት ወድቀናል
ተገልጠሽ አብሪልን ልጆችሽ ናፍቀናል
ሞትማ በሞት ተሸንፏል
በአንቺ ላይ እንዴት ኀይል ያገኛል፪
ድንግል ትንሣኤሽን እስከምናይ ድረስ
ገብተናል ሱባኤ በአንድነት በመንፈስ
ለኛ እስከ ሚገለጥ ቶማስ ያየው እውነት
አንወጣም ከደጅሽ ኪዳነ ምሕረት፪
ገብተናል ሱባኤ በአንድነት በመንፈስ
ለኛ እስከ ሚገለጥ ቶማስ ያየው እውነት
አንወጣም ከደጅሽ ኪዳነ ምሕረት፪
መዝሙረኛ አባትሽ ዳዊት ጽፎልናል
ሞትን የማያይ ሰው ማን አለ ብሎናል
ይህ እውነት በዘመን አንቺ ላይ ቢደርስም
በሞት ተሸንፈሽ መቃብር አትወርጂም
ሞትማ በሞት ተሸንፏል
በአንቺ ላይ እንዴት ኀይል ያገኛል፪
ሞትን የማያይ ሰው ማን አለ ብሎናል
ይህ እውነት በዘመን አንቺ ላይ ቢደርስም
በሞት ተሸንፈሽ መቃብር አትወርጂም
ሞትማ በሞት ተሸንፏል
በአንቺ ላይ እንዴት ኀይል ያገኛል፪
ድንግል ትንሣኤሽን እስከምናይ ድረስ
ገብተናል ሱባኤ በአንድነት በመንፈስ
ለኛ እስከ ሚገለጥ ቶማስ ያየው እውነት
አንወጣም ከደጅሽ ኪዳነ ምሕረት፪
ገብተናል ሱባኤ በአንድነት በመንፈስ
ለኛ እስከ ሚገለጥ ቶማስ ያየው እውነት
አንወጣም ከደጅሽ ኪዳነ ምሕረት፪
ቶማስ ከደመና ወርዶ ሲያናግረን
ስለሆነው ነገር እጅጉን ተመሰጥን
እኛም ይህን ክብር ተመኘን ለማየት
ድንግል አሳስቢልን ኪዳነ ምሕረት
ሞትማ በሞት ተሸንፏል
በአንቺ ላይ እንዴት ኀይል ያገኛል፪
ስለሆነው ነገር እጅጉን ተመሰጥን
እኛም ይህን ክብር ተመኘን ለማየት
ድንግል አሳስቢልን ኪዳነ ምሕረት
ሞትማ በሞት ተሸንፏል
በአንቺ ላይ እንዴት ኀይል ያገኛል፪
✦