እግዚአብሔር ፈቅዶ

እግዚአብሔር ፈቅዶ ዛሬ አንድ ሆነናል
እህቴ ሆይ ስሚ ማን ይለያየናል
ሥጋሽ ከሥጋዬ አጥንትሽ ከአጥንቴ
ተዋሕዶአልና ሆነሻል ሕይወቴ
በእመብርሃን ምልጃ በጌታ ቸርነት
በቃልህ ከታመንኩ በዚህ ቅዱስ እለት
የአጥንትህ ክፋይ አካልህ ነኝና
ጌታዬ ልበልህ ክብሬ አንተ ነህና
አንቺም ተጠበቂ ከዲያብሎስ ሴራ
ሰውነትሽ ዘወትር በጐ ምግባር ይሥራ
ቅድስና ወደሽ ከኃጢአት ራቂ
የሃይማኖትሸን ክር ማእተብሸን አጥብቂ
ከቃልህ አልወጣም ጌታዬ ሆይ ስማኝ
እስከመጨረሻው ፍጹም ታዛዥህ ነኝ
በቤተክርስቲያን ጥላ ስር በመሆን
በቃሉ እመራለሁ አንብቤ ወንጌልን
እግዚአብሔር ሆይ ስማን ቃልኪዳናችንን
ጋብቻችንን ባርክ ቀድስ ጐጆአችንን
ከዲያብሎስ ሴራ ጠብቀህ እኛን
እስከመጨረሻው በቃልህ አጽናን
← መዝሙር