እግዚአብሔርን ጠራሁት

እግዚአብሔርን ጠራሁት በኀዘኔ ጊዜ
እግዚአብሔርን ጠራሁት በጭንቀቴ ጊዜ
አወጣኝ ከጭንቀት ከሐዘን ከትካዜ /፪
የልመናዬን ድምጽ እርሱ ሰምቷልና
ጆሮውን ወደ እኔ አዝንብሏልና
በዘመኔ ሁሉ ስጠራው እኖራለሁ
ጎስቋላ ብሆንም ምስጋና አቀርባለሁ
እንደ ቃልህ መጓዝ መራመድ አቅቶኝ
የኃጢአቱ መንገድ ማእበሉ ገፍቶኝ
ወደ እርሱ ስማጸን ደግሞም ስጸጸት
አላሳፈረኝም መጣ በምሕረት
በበዛው ምሕረቱ ያለፈውን ትቶ
በፍቅሩ ጎበኘኝ አልተወኝም ከቶ
ሊቀበኝ ወዶ ፊቱን አበራልኝ
ማን ይቃወመኛል እግዚአብሔር ካለልኝ
ኖኅን አንዳዳንከው እኛንም አድነን
ከቀስቱ እንድናመልጥ ምልክትን ስጠን
በትርህ ምርኩዝህ እነርሱ ያጽናኑን
አንተ ከእኛ ጋር ነህ አንፈራም ክፉውን
← መዝሙር