እንደተቆጣኝ

እንደተቆጣኝ አልቀረም በርኅራኄ@ው ማረኝ
ቁጣውን መልሶ ለነፍሴ ለልቤ መጽናኛ ሰጠኝ
ምን ልክፈለው ለአምላክ ለወደደኝ
ልስገድለት ላመስግነው ኃይል ይስጠኝ
ዳገት ቁልቁለት በዛብኝ ለጽድቅ ወደአንተ ስጓዝ
ጠላት ተጠምጥሞ ከአንገቴ ጎንጎኔን ነደፈኝ በመርዝ
መፍትሔው< ጠፋብኝ ስቃይ በዛብኝ
አምላኬ ሆይ በጥበብህ አላቀኝ
ብቻኛ ነኝ ጭንቅ የያዘኝ የጠበበኝ
የዓለም ነፋስ ማእበሉ ያንገላ ኝ
መላም የለኝ እኔ ተክዤ ቆሜአለሁ
ኃይሌ ጉልበቴ መድኃኒቴ በለኝ አለሁ
ቆሜ ሳየው ፊት ኀእላዬን ቀኝ ግራዬን
ረዳት የለኝ ምርኩዝ የለኝ ነኝ ብቻዬን
የውስጥ የውጭውን ዘርዝሬ የምነግረው
እንደነፍሴ የምቆጥረው የማዋየው
አይተህ ይህን መጨነቄን መገፋቴን
ላክልኝ ለኔ ድንግልን እመቤቴን
ቅዱሳን ሰማእ ት ጻድቃን መላዕክትን
ፍጥረትህ ነኝ እንዳልጠፋ አትጨከን
የነበርክ ያለክ ለዘለዓለም የምትኖር
ከሥራዬ ባሳዝንህ ዘወትር
ያለረዳት አጽናኝ ብቻዬን ያልተውከኝ
ተስፋ አልቆርጥም ላመሰግንህ ፍቀድልኝ
← መዝሙር