እኔስ በምግባሬ

እኔስ በምግባሬ ደካማ ሆኛለሁ
እዘኝልኝ ድንግል እለምንሻለሁ
ያንን የእሳት ባሕር እንዳላይ አደራ
ድረሽልኝ ድንግል ስምሽን ስጠራ
የዳዊት መሰንቆ የኤልያስ መና
የናሆም መጽኃኒት ነይ በደመና
አንቺ ነሽ ጉልበቴ በደከመኝ ጊዜ
የልቤ መጽናኛ ረዳት ምርኩዜ
አፈሳለሁ እንባ በጣም ተጨንቄ
እማጸንሻለሁ በደሌን አውቄ
← መዝሙር