እስራኤል ሠለቸው

እስራኤል ሰለቸው የሰማዩ መና
ዓለም አምሮት ሄደ ጸጋውን ተወና
የእግዚአብሔር ስጦታ ኅብስቱ ስልችቶት
ዓለም አምሮት ሄደ ከተወው ባርነት
የፈርኦን ጅራፍ አልታየው አለ
የእህል አምሮቱን ውርደቱን ከለለ
ግብፅ ልሄድ ብሎ አመጸ በእግዚአብሔር
መድርሱ አልገባውም ከከነዓን ሀገር
የኪዳኑ ታቦት የሙሴ ገጽታ
ዓለም ስላማረው አደረገው ተርታ
የአምላክን ካህነት የአሮን ሥርዓት
በዓለም ለወጠው ትልቁን አምኃ
የኅብረቱን ጉዞ በፍቅር የሄደው
የማኅሌት ደስታ እስራኤል ታከተው
የእግዚአብሔርን ድንኳን ደመና ያጀባት
የኪዳኑን አርማ በበረሃ ተዋት
ዛሬም ይህ ትውልድ እስራኤልን ሆኗል
ቤክርስቲያኑን አምላኩን እረስቷል
ግብጽና ባቢሎን አጓጉተው ወስደውት
ወርቁን ከእጁ ጣለ መዳብ አስጎምጅቶት
← መዝሙር