እያለፈ ነው ዘመኔ

እያለፈ ነው ዘመኔ ትእዛዙን ሳልፈጽም ወየው ለእኔ
በጠራኝ ጊዜ ምን እላለሁ ና ብሎ ወደእኔ
በጠራኝ ጊዜ ምን እላለው ነይ ብሎ ወደ እኔ
በወጣትነቴ ሳልሠራ እያየሁ አለፈኝ ብዙ አዝመራ
ከእንግዲህ በመሥራት ጌታ ሆይ ልኑር ከአንተ ጋራ
የማስብበት በየለእቱ ንጹሕ ልብን ስጠኝ አቤቱ
ከትእዛዝህ ወጪ በመሆን እዳልቀር በከንቱ
እንደየሥራው ለመስጠት በግርማ መንግሥቱ ሲመጣ
ማን ይሆን የሚቆም ከፊቱ ፊተናን የወጣ
እንዳያስቷችሁ ተጠንቀቁ እየተማራችሁ ከቃሉ
ይመጣሉና በእርሱ ስም አምላክ ነን የሚሉ
ትእግሥትን በመያዝ ሁላችሁ እስከመጨረሻው ጠንክሩ
ያን ጊዜ ይሆናል በእርሱ ዘንድ የማዳን ተግባሩ
← መዝሙር