ፍቅርህ ማረከኝ

ፍቅርህ ማረከኝ በሕይወቴ በዘመኔ
እግዚአብሔር ለኔ መድኃኒቴ
ፍቅርህ ማረከኝ በሕይወቴ በዘመኔ
-------------------
ተገዝቻለሁ በወርቅ ደምህ
ዓለምን ትቼ ላገለግልህ
ሞትህ ሕይወቴ ለነ ሆኖኛል
ባንተ መከራ ሸክሜ እርቋል
ለክብርህ ቆሜ እዘምራለሁ
እንደ አቅሜ አገኝሃለሁ
…አዝ…
ምድርና ሰማይ እልል ይበሉ
ምስጋናም ላንተ ይድረስ እያሉ
መሳይ የለህም ለቅድስናህ
አቀርባለሁኝ ላንተ ምስጋና
ጣቴ በገና ይደረድራል
በቀን በሌሊት ያመሰግናል
…አዝ…
ክብርህን አይተው ጠላቶች ፈሩ
ለጌትነትህ ወድቀው ተገዙ
እንዲህ ነህ አምላክ እንዲህ ነህ ጌታ
ሁሉን በፍቅር የምትረታ
ባንተ ተመካሁ በፈጣሪያችን
አዳኝ በሆንከው በንጉሳችን
…አዝ…
← መዝሙር