ኃይልን በሚሠጠኝ
✦
ኃይልን በሚሠጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ፪
ፈተና ቢገጠግመኝ ለበጎ ነው ብዬ አልፋለሁ፪
በሠንሠለት አስረው በወኅኒ ቢጥሉኝ
መከራን አብዝተው እጅግ ቢያስጨንቁኝ
ለበጎ ነው ብዬ ተስፋ አድርጌሃለሁ
ይሁን አንተ ያልከው እገዛልሃለሁ
አዝ ---
ትናንትናም ዛሬም አንተ ያው አንተነህ
ፍቅርህ አይቀየር ወረትም የለብህ
ስምህን መጥራቴ ሞገስ ይሆነኛል
ጠላቴ ቢፎክር መቼ ያሸንፈኛል
አዝ ---
በመከራው ብዛት ጉልበቴ ደከመ
ትካዜ ከብዶኛል ተስፋዬም ጨለመ
ነገር ቢሆን ባይሆን አንተን እንዳከብር
ፈተና ቢገጠግመኝ ለበጎ ነው ብዬ አልፋለሁ፪
በሠንሠለት አስረው በወኅኒ ቢጥሉኝ
መከራን አብዝተው እጅግ ቢያስጨንቁኝ
ለበጎ ነው ብዬ ተስፋ አድርጌሃለሁ
ይሁን አንተ ያልከው እገዛልሃለሁ
አዝ ---
ትናንትናም ዛሬም አንተ ያው አንተነህ
ፍቅርህ አይቀየር ወረትም የለብህ
ስምህን መጥራቴ ሞገስ ይሆነኛል
ጠላቴ ቢፎክር መቼ ያሸንፈኛል
አዝ ---
በመከራው ብዛት ጉልበቴ ደከመ
ትካዜ ከብዶኛል ተስፋዬም ጨለመ
ነገር ቢሆን ባይሆን አንተን እንዳከብር
አድለኝ በጸጋ ጌታ የአንተን ፍቅር
አዝ ---
ከሀገር ተጥቼ በዱር መሠደዴ
በባእዳን ሀገር ርቄ መሄዴ
ለበጎ ነውና መቼ ይከፋኛል
ፈጽሞ እንዳልጠፋ ፍቅርህ ይይዘኛል
አዝ ---
አዝ ---
ከሀገር ተጥቼ በዱር መሠደዴ
በባእዳን ሀገር ርቄ መሄዴ
ለበጎ ነውና መቼ ይከፋኛል
ፈጽሞ እንዳልጠፋ ፍቅርህ ይይዘኛል
አዝ ---
✦