ሁለቱም አንድ ሆኑ ዛሬ

ሁለቱም አንድ ሆኑ ዛሬ
በእግዚአብሔር በሕያው ቃሉ
ሁለቱም አንድ ሆኑ ዛሬ
አዝ ---
ወንድና ሴት አድርጐ እንደፈጠራቸው
በኋላም በቃሉ አንድ አደረጋቸው
እናትና አባቱን የአዳም ልጅ ይተዋል
ከሚስቱ ጋር በሰላም በአንድ ይተባበራል
አዝ ---
ሁለቱም አንድ ሥጋ ሆነው ይኖራሉ
ብሎ አስተምሮናል ጌታችን በቃሉ
አንድ ሥጋ ናቸው አይደሉም ሁለት
የባልና የሚስት ሕይወት ወደፊት
አዝ ---
እንግዲህ እግዚአብሔር ካጣመራችሁ
በሆነው ባልሆነው ሰው አይለያችሁ
ለወገኖቻችሁ ምሣሌ ሆናችሁ
በክርስትና ፍቅር አምላክ ያኑራችሁ
አዝ ---
ምንጣፋችሁ ብሩህ መኝታችሁ ንጹህ
ስለሆነላችሁ እንኳን ደስ አላችሁ
ዓለም እንዲደነቅ ሰይጣን እንዲያፍር
በሐዘን በደስታ ይኑራችሁ ፍቅር
አዝ ---
← መዝሙር