ከሰዎች ማነው

ከሰዎች ማነው እንደ እኔ ትእዛዝህን ሻሪ
ከአማልክትስ ማነው እንዳተ መሀሪ
የኃጢያት ሸክም ከብዶብኝ ሲያስጨንቀኝ
ጠላቶች ከብበው በኔ ላይ ስዝቱብኝ
ብቸኝነቴን አይተህ ስለደረስክልኝ
ተመስገን እንጂ ላንተ ሌላ ምን አለኝ
አዝ ---
በደሌን አይተህ በቅጽበት ያላጠፋኸኝ
እንደ ጥፋቴ በቁጣ ያልተበቀልከኝ
ቸር እና የዋህ አምላክ እንደ አንተ ማን ይገኝ
አዝ ---
እንደ ሕዝቅያስ ጸሎቴን አምላክ ስማኝ
እንደ ዳዊትም ልመናዬን ተቀበለኝ
በዘመኔ እኩሌታ አምላኬ አትውሰደኝ
ወሰን በሌላት ፍቅርህ ታግሰህ ጠብቀኝ
አዝ ---
← መዝሙር