ላይቀር መሞት

ላይቀር መሞት አፈር መልበስ መግባት ከመቃብር
መስሎኝ ቋሚ ይህ ሥጋዬ ለእርሱ ብቻ ስጥር
ግን ለነፍሴ ቀረ ማስታወሴ
ዘመን መቁጠር እለት ወራት ክረምትና በጋ
ሌትና ቀን ሲፈራረቅ ሲጨልም ሲነጋ
በማየቴ ይሆን መደሰቴ
ኸረ ወዲያ ወዲያልኝ ዋይ ይብላኝ ለነፍሴ
አድርጎኛል የኃጢአት ምንጭ ደካማው መንፈሴ
ላልኖር በዓለም ቆሜ ለዘለዓለም
መሐሪ አምላክ ለጋስ ጌታ ቸሩ ፈጣሪዬ
አንተ እኮ ነህ ለዘለዓለም ለእኔ መመኪያዬ
ይቅር በለኝ ምሕረትህ አይራቀኝ
← መዝሙር