ለነፍሴ ነፍሷ ነሽ
✦
ለነፍሴ ነፍሷ ነሽ ለመንገዴ ፋና
እንዳልጠፋ አምናለሁ የአንቺ ልጅ ነኝና፬
------------------------------
የፃድቃን እናቶች እጅግ ብዙ ናቸው
ከብሉይ ከሃዲስ ብንዘረዝራቸው
አንቺ ግን አንዲት ነሽ የለሽም ጭማሪ
ትኖሪያለሽ እንጂ ትውልድ ስታስምሪ
እንዳልጠፋ አምናለሁ የአንቺ ልጅ ነኝና፬
------------------------------
የፃድቃን እናቶች እጅግ ብዙ ናቸው
ከብሉይ ከሃዲስ ብንዘረዝራቸው
አንቺ ግን አንዲት ነሽ የለሽም ጭማሪ
ትኖሪያለሽ እንጂ ትውልድ ስታስምሪ
ለነፍሴ ነፍሷ ነሽ ለመንገዴ ፋና
እንዳልጠፋ አምናለሁ የአንቺ ልጅ ነኝና፬
------------------------------
ያንቺን ሥም ተማጽኖ ያንቺን ሥም ቀድሶ
አንቺን አመስግኖ አንቺን አወድሶ
የተጠቀመ እንጂ በረከት አግኝቶ
አልታየም እስካሁን የተጎዳ ከቶ
እንዳልጠፋ አምናለሁ የአንቺ ልጅ ነኝና፬
------------------------------
ያንቺን ሥም ተማጽኖ ያንቺን ሥም ቀድሶ
አንቺን አመስግኖ አንቺን አወድሶ
የተጠቀመ እንጂ በረከት አግኝቶ
አልታየም እስካሁን የተጎዳ ከቶ
ለነፍሴ ነፍሷ ነሽ ለመንገዴ ፋና
እንዳልጠፋ አምናለሁ የአንቺ ልጅ ነኝና፬
------------------------------
ጎርጎርዮስና ሊቁ ዮሐንስ
አትናቴዎስና ሊቁ ባስልዮስ
አባ ኤፍሬምና አባ ጊዮርጊስ
ተጠቅመዋል በአንቺ በሥጋም በነፍስ
እንዳልጠፋ አምናለሁ የአንቺ ልጅ ነኝና፬
------------------------------
ጎርጎርዮስና ሊቁ ዮሐንስ
አትናቴዎስና ሊቁ ባስልዮስ
አባ ኤፍሬምና አባ ጊዮርጊስ
ተጠቅመዋል በአንቺ በሥጋም በነፍስ
ለነፍሴ ነፍሷ ነሽ ለመንገዴ ፋና
እንዳልጠፋ አምናለሁ የአንቺ ልጅ ነኝና፬
------------------------------
አባትህን ጠይቅ ስለሚለን ቃሉ
ብንጠይቃቸው ቅዱሳኑን ሁሉ
ስላንቺ ነገሩን ክብር ተዓምራትሽን
ለሰው ዘር በሙሉ አማላጅ መሆንሽን
እንዳልጠፋ አምናለሁ የአንቺ ልጅ ነኝና፬
------------------------------
አባትህን ጠይቅ ስለሚለን ቃሉ
ብንጠይቃቸው ቅዱሳኑን ሁሉ
ስላንቺ ነገሩን ክብር ተዓምራትሽን
ለሰው ዘር በሙሉ አማላጅ መሆንሽን
ለነፍሴ ነፍሷ ነሽ ለመንገዴ ፋና
እንዳልጠፋ አምናለሁ የአንቺ ልጅ ነኝና፬
------------------------------
ገብርኤል ከሰማይ ኤልሳቤጥ ከምድር
በአንድ መሠከሩ ስለ ድንግል ክብር
ሰዓሊ ለነ ብሎ ተማጽኖ በአንቺ ስም
የተጠቀመ እንጂ የተጎዳ የለም
እንዳልጠፋ አምናለሁ የአንቺ ልጅ ነኝና፬
------------------------------
ገብርኤል ከሰማይ ኤልሳቤጥ ከምድር
በአንድ መሠከሩ ስለ ድንግል ክብር
ሰዓሊ ለነ ብሎ ተማጽኖ በአንቺ ስም
የተጠቀመ እንጂ የተጎዳ የለም
ለነፍሴ ነፍሷ ነሽ ለመንገዴ ፋና
እንዳልጠፋ አምናለሁ የአንቺ ልጅ ነኝና፬
እንዳልጠፋ አምናለሁ የአንቺ ልጅ ነኝና፬
✦