ለንስሓ ሞት አብቃኝ

ለንስሓ ሞት ቷብቃኝ
በሂሶኘ እርጨኝ እጠበኝ
እንደ በረዶ አንሳኝ
አመፃዬ በዛ ኃጢአትን ጨመርኩኝ
ልቤ ደነደነ ክፋትን ፈጸምኩኝ
እንደ ፈርዖን ልቤ እንዳይጸናብኝ
አድነኝ እንደ ኖኅ አምላክ ራራልኝ
አድነኝ ስለ ድንግል ብለህ አድነኝ
አድነኝ ስለ ሳድቃን ብለህ አድነኝ
አዝ ፥ ፥ ፥ ፥ ፥ ፥
ኃጢአቴም በረታ ሰለጠነብኝ
ከቃልህ አስወጣኝ ሕግህን ጣስኩኝ
እንደነነዌ& ሕዝብ ንስሓን ስጠኝ
ምሕረትህን ልከህ ልቤን ስበርልኝ
አድነኝ እንደ ቸርነትህ አድነኝ
አድነኝ እንደ ምሕረትህ አድነኝ
አዝ ፥ ፥ ፥ ፥ ፥ ፥
ያደፈዉ ገላዬን አንተ አጥራልኝ
ከሰዶም ገሞራ እንዳይብስብኝ
መንገድና ሕይወት አንተ ነህ ምራኝ
የቅዱስ ጴጥሮስን ንስሓ ስጠኝ
አድነኝ እንደ ቸርነትህ አድነኝ
አድነኝ ስለ እናትህ ብለህ አድነኝ
አድነኝ ስለ ሳድቃን ብለህ አድነኝ
← መዝሙር