መድኃኔዓለም

መድኃኔዓለም ዘቆምክ በቅደመ ጲላጦስ
መድኃኔዓለም ዘቆምከ በዓውደ ሄሮድስ
ቀራንዮ በዚያ ቦታ
ቀራንዮ ምድረ ጎልጎታ
እጅ እግርህ ታሥረህ በራስህ ፈቃድ
ተገፋህ ተንገላታህ በእደ አይሁድ
ለሸክም ዳረጉህ ለማይቻል ግንድ
እናትህ ስታለቅስ ስለ አንተ መከራ
በቀኖት ሲወጉህ ደምህም ሲዘራ
የራሔልም ልቅሶ በነርሱ ደረሰ
ኀዘን ተሰማቸው ዕንባቸው ፈሰሰ
አይሁድ ባሰባቸው ያዛቸው ጭካኔ
ምራቅን ተፉበት ገረፉት ወይኔ
ዳዊት በገናውን እየደረደረ
አገቱኒ ብሎ ትንቢት ተናገረ
ዘማሪ በየነ ድንቁ
← መዝሙር