መስክሪ ቀራንዮ 1

መስክሪ ቀራንዮ መስክሪ ጎልጎታ
›› ›› ›› ሊቶስጥራ
የተቀበለውን የአምላክን መከራ
ሊሰቅሉት ሲወስዱት መስቀል አሸክመው
ስምኦን ቀሬናዊ ከመንገድ አገኘው
ከድካሙ ብዛት ሳይሰሉት እንዳይሞት
ለቀሬናዊ ሰው ስሞኦን መስቀል አሸክሙት
የአምላክን ትእግሥት በማየት ተደንቆ
ጲላጦስ ጠየቀው እንዲፈታው አውቆ
ጌታም መለሰለት ከላይ ካልተሰጠ
በእኔ ላይ ልትፈርድ አንዳች ኃይል የለህ
ስቀለው እያሉ ባንድ ላይ ሲጮሁ
ጲላጦስ ጨነቀው የሚያደርገው ጠፋው
ከደሙ ንጽሕ ነኝ በማለት ታጠበ
የጌታን ንግግር ቃሉንም አሰበ
መከራ መስቀልህ ሲነገር ይጨንቃል ነፍስም
ትርዳለች ሥጋንም ይዳከማል
ድካምህን ሁሉ ከንቱ እንዳላደርገው
በንስሓ እንባ ኃጢአቴን እጠበው /
← መዝሙር