መጽሐፍ ቅዱስን

መጽሐፍቅዱስን ሁሉም ያነበዋል
ምእራፍና ቁጥሩን ሁሉም ይጠቅሰዋል
በዚህ ብቻ አይበቃም ተርጓሚ ያሻዋል
እንደፈቃዳችን ብንተረጉመው
በውጥን የሚልቀው ስህተቱ ብዙ ነው
ከቶ በሰው ፈቃድ ትንቢት እንዳልመጣ
ይነግረናል መጽሐፍ ከሕግ እንዳንወጣ
ይመክረናል መጽሐፍ ከሕግ እንዳንወጣ
እንጠይቅ መምህራን ያሉት በደረጃ
እናንብብ መጽሐፍት ይሁኑን ማስረጃ
← መዝሙር