ምደረ ቀራኒዮ

ምደረ ቀረንዮ ምደረ ጎልጎታ
መድኃኒት ክርስቶስ በአንቺ ተንገላታ
መስክሪ አንቺ ምድር ግኡዚቷ ሥፍራ
መድኃኒት ክርስቶስ ያየብሽን መከራ
ደሙ እንደውኃ ሲፈስ መስቀሉ2/
በቀራንዮ ቦታ መከራውን ሲያይ
ፀሐይ ከለከለች ደማቅ ብርሃኗን
ለመሸፈን ብላ የአምላክን እርቃን
በመስቀል ተሰቅሎ ፍቅሩን ገለጸው
በመስቀል ላይ ሆኖ ተጠማሁ እያለ
የሾህ አክሊል ደፍቶ ቀራንዮ ዋለ
እጆቹን እግሮቹን በችንካር ተመተው
ቸሩ መድኃኔዓም እባክህ ማረን/
ደካሞች ነንና እንዳንቀር ጠፍተን
በቆረሰከው ስጋ ባፈሰሰከው ደም
አቤቱ ተራዳ እስከ ዘላለም
← መዝሙር