ምድር ጸዳች

ምድር ጸዳች ሐሴት አደረገች
ምድር ጸዳች ከእድፍም ነጻች
በክርስቶስ ደም በእውነት ጠበች
ሴቶች ትንሣኤውን ሲያወሩ በደስ
ሟሐ ስትመሰክር ምድር አፍዋን ከፍ
የተዘጋው ዓለም ሲገለባበጥ
ምን ተናገሩ አይሁድ ከፍርድ ለማምለጥ
አያልቅባቸውም የእነርሱ ፈሊጥ
መግነዙ ተገኘ ከመቃብር ወድቆ
ምልክት እንዲሆን ተወላቸው አውቆ
እሑድ በማለዳ መቃብሩን ሲያዩ
ሁሉም ተለውጦ ልቅሶው ደስ ሆነ
ሁለቱ መላእክት ብርሃን የለበሱ
ተነሥቷል አሏቸው ሴቶቹ ሲደርሱ
ሐዋርያት ሰምተው ዜና ትንሣኤውን አላቸው በድንገት ሰላም ለእናንተ ይሁን
← መዝሙር