ምን ሰማህ ዮሐንስ

ምን ሰማህ ዮሐንስ /በማሕፀን ሳለህ /
ሕፃን ሆነህ ነቢይ /ለክብር የተጠራህ /
እንደ እንቦሳ ጥጃ/ያዘለለህ ደስታ/
ምን ዓይነት ድምፅ ነው /ምን አይነት ሰላምታ/
ከተፈጥሮ በላይ ያሰገደህ ክብር
እንዴት ቢገባህ ነው/የእናታችን ፍቅር /
ሌላ ድምፅ አልሰማም ከእንግዲህ በኋላ
ለውጦኛልና /የሰላምታ ቃሏ /
አዝ......
በረሃ ያስገባህ ለብዙ ዘመናት
ምን ያለ ራዕይ /እንዴት ያለ ብሥራት/
አንደ አዲስ ምስጋና ስልቱ የተዋበ
ተደምጦ የማያውቅ/ጭራሽ ያልታሰበ /
አዝ.......
ከሴት ከተገኙ ከደቂቀ አዳም
ድንግል ስለሆነ /በሕይወቱ ፍጹም/
ከማሕፀን ሳለ ተመርጦ በጌታ
ለማዳመጥ በቃ የኪዳን ሰላምታ/
← መዝሙር