ምስጋናዬ ለአምላኬ አቀርባለሁ

ምስጋናዬ ለአምላኬ አቀርባለሁ
በማደርያው ገብቼ እስግድለታለሁ
ኤልሻዳይ ነው ጌታ ሁሉን ቻይ
ይፈፀማል አምናለሁ የልቤ ጉዳይ
አ.ዝ================
ዘንባባዬን ይዤ እንደ ህፃናቱ
ሆሳህና ልበለው ሰግጄ በፌቱ
ምንም ባዶ ብሆን እውቀት ቢጎለኝ
ለስሙ ልዘምር ከልካይም የለኝ
አ.ዝ================
አምላኬ በፌትህ ቃል አለብኝ እኔ
ቋንቋዬ መዝሙር ነው ያንተ እንደመሆኔ
በአሚናዳብ ደጃፍ በቅድመ ታቦቱ
ያየክብርህ ሁደት ጠራኝ ማህሌቱ
አ.ዝ===============
የህይወት ትርጉሜ አንተ ነህ ደስታዬ
ስምህን ማገልገል ክብሬ ነው ስራዬ
ለታመነው ጌታ ምስክር የሆኑ
ከብረው ተመለሱ ለበረከት ሆኑ
አ.ዝ================
መነሻዬ አንተ ነህ ጉልበቴና ክብሬ
መድረሻዬም አንተ መደምደሚያ ቅጥሬ
በፅዮን ተራራ ስትገለጥ ያኔ
ነጩን ልብስ አልብሰህ አስነሳኝ ለቅኔ/፪
← መዝሙር