ሞቼ ስለማልቀር

ሞቼ ስለማልቀር ትንሣኤ ስላለኝ
በተስፋ ቤታችን ስለምንገኛኝ
ወዳጅ ዘመዶቼ አታልቅሱ በቃኝ
አቀናለሁና ገና አዲስ ኑሮ
አምላክን አስቡት ይብቃችሁ እሮሮ
ይልቅ ጸልዮላት ለነፍሴ እረፍት
ዓለም አታላይ ናት ዘላቂ አይደለች
ለሥጋ ነው እንጂ ለነፍስ አትመች
ግን ከሥጋ ጋር ስንኖር ትእዛዙን ከጠበቅን
ለተዘጋጀው ቤት ወራሾች እኛው ነን
መቼም ከማያልቀው በረከት ያደልከን
ዘላለማዊ ሕይወት ለሰጠኽኝ
ምስጋናችን ይድረስህ ጸጋህ አይለየን
እኛ በድለን ትህዛዝህን ጥሰን
አንተ በመስቀል ላይ ደምህ ፈሰሰልን
ፍቅርህን ስናስብ እጅግ ይደንቀናል
ለዚህ ሁሉ ውለታህ ምን እንከፍላለን
← መዝሙር