ነፍሴ ሆይ

ነፍሴ ሆይ እግዚአብሔርን በቅን አገልግይ
የተቀበለው በቀራንዮ
ያን ሁሉ መከራ በመስቀሉ ላይ
ለአንቺ ሲል ነውና ነፍሴ ሆይ
ተዘጋጅተሸ ኑሪ ሁልጊዜ
በነገ በዛሬ እንዳትታለዪ ነፍሴ ሆይ
በንስሓ ጥምቀት ታጠቢና
ክቡር ደሙን ጠጪ ሥጋውንም ብይ
ነፍሴ ሆይ
ዘላለም በደስታ እንድትኖሪ
ከዘላለም ቤትሽ መንግሥተ ሰማይ
ነፍሴ ሆይ
← መዝሙር