ንዓ አማኑኤል

ንዓ ንዓ አማኑኤል
ንዓ ንዓ መድኃኔዓለም
በፍሥሐ ወበሰላም
ና ወደኛ መድኃኔዓለም
ቅዱስ ጌታ አማኑኤል
ቸር አምላክ መድኃኔዓለም
ለእኛ ብለህ አማኑኤል
ተሠቀልክ መድኃኔዓለም
ልትባርከን አማኑኤል
ና በሰርክ መድኃኔዓለም
አዝ ---
ሥጋህና አማኑኤል
ደምህን መድኃኔዓለም
ብሉ ብለህ አማኑኤል
ሠጠኸን መድኃኔዓለም
ሕይወትህ ሆኖ አማኑኤል
አዳነን መድኃኔዓለም
አዝ ---
በኃጢአት ሞት አማኑኤል
ወድቀን ሣለ መድኃኔዓለም
ከጥንት ሀገር አማኑኤል
ኑ አልከን መድኃኔዓለም
ምንስ እንበል አማኑኤል
ምን እናውራ መድኃኔዓለም
ግሩም ብቻ አማኑኤል
ያንተ ስራ መድኃኔዓለም
አዝ ---
← መዝሙር