ቅዱስ ገብርኤል እርዳን

ቅዱስ ገብርኤል ርዳን ሊቀ መላእክት
ልጆችህን አውጣን ከሚነድ እሳት
ልጆችህን አውጣን ከዓለም እሳት
ከማይጠፋው እሳት ከዚያ ነበልባል
ከጨለማው ሥርዓት ከክፉ ሲኦል
ነፍሳችንን ነጥቆ ሰይጣን እንዳይጎዳን
ዋስ ጠበቃ ሁነን ቅዱስ ገብርኤል ርዳን
ረድኤት በረከትን ጸጋህ አይለየን
እንለምንሃለን አደራ እንዳትርቀን
የቀደመው ጠላት ዙሪያችን ከቦናል
ቅዱስ ገብርኤል ድረስ የእግዚአብሔር ባለሟል
ናቡከደነጾር ገደል ሲከታች
እሳቱን አንድዶ ከእሳት ቢጥላቸው
ከራሳቸው ፀጉር አንድ እንኳን ሳይጠፋ
ቅዱስ ገብርኤል ደርሶ ሆነላቸው ተስፋ
ብቸኝነት ከብዶን ሐዘን ሲያስጨንቀን
እኛ እንጠራሃለን ቅዱስ ገብርኤል ብለን
በፈጣሪያችን ፊት ስለእኛ ቆመሀል
የነደደብንን እሳት አብርደሃል
ሥልጣንህ ግሩም ነው በአምላክህ ፊት
እንሠግድልሀለን የጸጋ ስግደት
ፈጥነህ የምትሰማን ወዳንተ ስንጮህ
.................................................... - 132 -
የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ነህ
አዝ ----
← መዝሙር