ሰው ለሰው

ሰው ለሰው ቢፋቀር ምነው
ለሰው ይመስለዋል ብዙ የሚቆይ
ግን በድንገት ያልፋል ሁሉንም ሳያይ
ሀብትን ከማቻል ቀኑን ሳውቀው
በድንገት ይጠራል አይከተለውም
የሰው ልጅ በተራ መጠራቱ ላይቀር
ምነው አንዱ ለአንዱ መቃብር ባይቆፍር
አይጠቅምም መጨነቅ እንዲያው ለውበት
ይረግፋል ይጠፋል ሁሉም ከመሬት
ዋ ቁንጅና ከንቱ ማማርም ብላሽ
አፈር ትቢያ ሲሆን ሲጨለምሲመሽ
ደሀ ባለጸጋ አንድ ነው መንገዱ
በጨርቅ ተገንዞ በሳጥን መሄዱ
ሰው ዙሪያውን ቢያጥር መዝጊውን ቢሠራ
በሕንፃ ላይ ሕንፃ ቢያስመስል ተራራ
አይቀርም መሄዱ ሁሉም በየተራ
← መዝሙር