ጥምቀተ ባሕር
✦
ጥምቀተ ባሕር ዮርዳኖስ ነያ፪
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፪
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፪
ጌታችን ሲጠመቅ ባሕር ምን አለች
አልችለውም ብላ ወደ ኋላ ሸሸች
ብርሃነ መለኮት በወንዞች ሲሞላ
ዮርዳኖስም ሸሸ ቀረ ወደ ኋላ
አዝ = = = = =
አብ በመጣ ጊዜ ደመናውን ጭኖ
መንፈስ ቅዱስ ታየ በርግብ አምሳል ሆኖ
ለልጁ ምስክር ሊሆን ፈለገና
ቃሉን ተናገረ ሆኖ በደመና
አዝ = = = = =
ጌታችን ሲጠመቅ በሰላሳ ዓመት
ባህር ኮበለለች ግዑዟ ፍጥረት
ሰማይ ተከፈተ ሆነልን ፀአዳ
ምስጢረ ሥላሴ ታወቀ ተረዳ
አዝ = = = = =
እልል በይ ዮርዳኖስ የጥምቀት መገኛ
የፅድቅ መሰላል ድህነታችን ለኛ
ቀላያት አብርህት ብዙዎች እያሉ
እንደምን ተመረጥሽ ዮርዳኖስ ከሁሉ
አልችለውም ብላ ወደ ኋላ ሸሸች
ብርሃነ መለኮት በወንዞች ሲሞላ
ዮርዳኖስም ሸሸ ቀረ ወደ ኋላ
አዝ = = = = =
አብ በመጣ ጊዜ ደመናውን ጭኖ
መንፈስ ቅዱስ ታየ በርግብ አምሳል ሆኖ
ለልጁ ምስክር ሊሆን ፈለገና
ቃሉን ተናገረ ሆኖ በደመና
አዝ = = = = =
ጌታችን ሲጠመቅ በሰላሳ ዓመት
ባህር ኮበለለች ግዑዟ ፍጥረት
ሰማይ ተከፈተ ሆነልን ፀአዳ
ምስጢረ ሥላሴ ታወቀ ተረዳ
አዝ = = = = =
እልል በይ ዮርዳኖስ የጥምቀት መገኛ
የፅድቅ መሰላል ድህነታችን ለኛ
ቀላያት አብርህት ብዙዎች እያሉ
እንደምን ተመረጥሽ ዮርዳኖስ ከሁሉ
✦